የሐራጅ ማስታወቂያ
ዘምዘም ባንክ አ/ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ቀጥሎ ባለው ሰንጠረዥ ውስጥ የተመለከቱትን በመያዣነት የያዛቸውን ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ሐራጅ መሸጥ ይፈልጋል።
| ተ.ቁ | የተበዳሪ ስም | የመያዣ ሰጪ ስም | የካርታ ቁጥር | የሚገኝበት ቦታ | የቦታው ስፋት | የጨረታ መነሻ ዋጋ | የጨረታ ቀንና ሰዓት | ጨረታው የወጣው | |
| 1. | ወ/ሮ መኪያ ከድር | አቶ አበራ አብደላ | AA000090711021 | አዲስ አበባ ኮልፌ ቀ/ክ/ከ የቤት ቁጥር | 382 ካሬ ሜ. ላይ ያረፈ B+G+10 ህንጻ | 25,991,734.85 | 11/02/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 2. | አቶ ሀሚድ ሀሰን | ወ/ሮ ዘይነባ መሀመድ | ወ3/ውዝ/01/557/13880/03 | አዲስ አበባ ኮልፌ ቀ/ክ/ከ ወረዳ 3 | 1264 ካ.ሜ G+1 መኖሪያ ቤት | 11,219,484.35 | 12/02/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 3. | ዶ/ር ሰይድ ሁሴን አሊ | ዶ/ር ሰይድ ሁሴን አሊ | A-26319/09 | አማራ ብ/ክ/መ/ ደሴ ከተማ ቀበሌ 10 | 335 ካ.ሜ ላይ ያረፈ B+G+1 የንግድ ማአከል | 4,932,965.33 | 17/02/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 4. | አቶ አባይነህ ተስፋዬ | አቶ አባይነህ ተስፋዬ | 306/BMG/2016 | ም/ጉጂ ዞን ጉዋንጉዋ ከተማ | 210.30 ካ.ሜ. መኖሪያ ቤት | 2,756,882.30 | 24/02/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 5. | አቶ አህመድ አራጌ | አቶ አህመድ አራጌ | A=6898 | አማራ ብ/ክ/መ/ ደሴ ከተማ መናፈሻ ክ/ከተማ | 150 ካ.ሜ ላይ ያረፈ B+G+1 የንግድ ማአከል | 1,557,362.57 | 17/02/2018 | ከ 8፡00 – 11፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 6. | አቶ ኡስማን ሙሀመድ | አቶ ኡስማን ሙሀመድ | ሠ/ሎ/ክ/ከ/አ/365/2014 | አፋር ብ/ክ/መ/ ሰመራ-ሎጊያ ከተማ | 446.25 ካ.ሜ. መኖሪያ ቤት | 361,556.65 | 1/03/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 7. | አቶ ቶፊቅ ሸምሱ | አቶ በክረዲን ተመስገን | እ/ክ/ማ/113/2014 | ወልቂጤ ከተማ | 200 ካ.ሜ መኖሪያ ቤት | 596,200.01 | 08/03/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለመጀመሪያጊዜ |
| 8. | አቶ ከድር አብደላ ኢብሮ | አቶ ከድር አብደላ ኢብሮ | መ/ከ/ማ/55/07 | ስልጤ ዞን መናሃሪያ ከተማ | 918 ካ.ሜ መኖሪያ ቤት | 201,829.17 | 09/03/2018 | ከጠዋቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት | ለሶስተኛ ጊዜ |
- ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ኛ በተረጋገጠ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) በዘምዘም ባንክ (አ/ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ፀድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል፤ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ በሲ.ፒ.ኦ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውንም ወጪዎች እና ውዝፍ የሊዝ ዕዳዎችን ይከፍላል፡፡
- ሐራጁ የሚከናወነው ንብረቶቹ በሚገኙበት አድራሻ ይሆናል ነው።
- ተበዳሪዎች እና ንብረት አስያዦች ወይም ሕጋዊ ተወካዮች የጨረታውን ሒደት ለመከታተል ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ቦታ እንድትገኙ እያሳሰብን ካልተገኛችሁ በሌላችሁበት ጨረታው የሚከናወን መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ባንኩ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ወይም ተጫራቾች ቤቶቹን ለመጎብኘት ቀጠሮ ለማስያዝ በስልክ ቁጥር +251 11 5582308 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
ዘምዘም ባንክ አ/ማ



